የታሪክ ማስታወሻ
የዚህ ታሪክ ጸሐፊ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ (ብላታ) መጋቢት 17 ቀን 1891 ዓ.ም. ሸዋ ጅሩ ውስጥ እምቧጮ መግደላዊት በተባለ ስፍራ ተወለዱ። አባታቸው አለቃ ወልደ ቂርቆስ አልታመን ይባላሉ። እሳቸውም በደብረ ሊባኖስና በእንጦጦ ማርያም የቤተ ልሔምን መዝገበ ድጓ ሲያስተምሩ የነበሩና በዜማ መምህርነት የታወቁ ናቸው።
በብላታ መርስዔ ኀዘን የተደረሱና የተዘጋጁ
ትምህርተ ሕፃናት፣ 1917 ዓ.ም.
የአማርኛ ሰዋስው በአዲስ ሥርዓት የተሰናዳ፣ 1935 ዓ.ም.